Saturday, September 26, 2009
Abesha phone line stories.
Monday, June 29, 2009
The new Habesha line.
It was kind of rude awakening to hear that how many people have ample time to trash out one another. 75-80 percent in my view were some how "i missed the right turn and up here so let me out types." Didn't leave immediately, rather i stayed and tune in for whatever is on the menu. Half an hour later shoked and surprized left the line. For the next two three days keep coming start to enjoy whatever hopping from line to line. Came accross through different caracters not all of them were shoking but somehow.....Ooooooooo Weeeeeeeeeeeeee.
One of these days i will start posting my observations on weekly or dayly basis. For now check you later.
The king has moved on.
A sad day for our planet. I was at work while hearing this crushing news Michael Jackson has gone. For me or all the fans The great MJ is in our hearts.He will live forever. He was our God's gift. He is super nature, pure spirit and full of love.
He awaken our eyes to the beauty of nature, the urge to listen through the heart and flow with the beautiful music.He did everything to make us feel his love and God's presense. While devastated i over heard someone saying "Michael Jackson has nothing to proof to the world. He has finished his job on earth and moved on." Seems hard for the fans but it has some truth in it. Let's think about all MJ's songs and artistic performance.He has changed us for the better beyond all human made barriers, color, race, culture and what have you.He was the greatest yester day, He is the Great one today and He will be the Greatest for Eternity.
MAY HIS SOUL REST IN PEACE
Friday, June 12, 2009
11
ህይወት ክፍል 11
የሰው ልጅ በኖረባቸው ብዙ ሺኅ ዓመታት በተፈጥሮ ያደረገው ዝግመታዊ ለውጥና ከተፈጥሮ ጋር ባደረገው ፍጥጫ የደረሰባቸው የቴክኖሎጂ ውጪቶች የሚያስደንቁን ቢንም እንዳንድ ጊዜ ገን ግራ እያጋቡን ይጋኛሉ፡፡
ከቻርሊስ ዳር ዊን ቴዎሪ ተነስተን የሰውን ልጅ በራሱ ላይ በተፈጥሮ ክስተቶች በመታገዝ ያደረገውን ዝግመት ለውጥ ሰናይ በማህበረሰብ በመሰባሰበብ ያሳለፈውን ህይወትና የማህበረሰቡን የዕድገት ደረጃ እንደናጢን መገደዳችን አሌ አይባልም፡፡
በኢትዮጵያችን እንኳ ባሪያ መሸጥ መለወጥ እንዲቆም በአዋጅ ደረጃ /በተገበር ላይ ከአዋጁ በኋላም ቆቶ ተሰተዋሏልና፡፡/ በአፄ ሚኒሊክ ጊዜ ነው የተደረገገው፡፡ /ይህ የባሪያ ፍንግሌ ግን በዘመናዊ መልክ ቀጥሎ የመኖር እስትንፋሱ በተወሰነ ደረጃ ቀይሮ ባሪያ የነበረው ሠራተኛ ተሰጥቶ ይገኛል፡፡/ እዚህ ላይ አማረኛ ቋንቋ ስሚችግረኝ ለቃላት አጠቃቀሜ እንባቢን ይቅርታ እጠይቃለሁ፡፡/
በቴክኖሎጂና ብሔራዊ ሀብት መጠን በልፀገዋል በሚባሉት ሀገሮች ሁሉ የባሪያ ፍንግሌ /ያላችሁትን በሉኝ እንጂ/ እንደቀጠለ ነው ያለው፡፡ እዚህ ላይ ምሳሌ ብጠቅስ ሃሳቤን ግልፅ ያደርገዋልና እንካችሁ፡፡
ለሞኑን የዓለም ዋንጫ እተካሄደ ነው፡፡ እኔ እንኳን ጥሩ የእግር ኳስ ጥበብ ለማየት ብቻ ሰምቼ እያለሁ እንጂ በቀን በቀን የአንቀጽ ልፍ ሰዓቱን እንዲሻብብቅ አልፈልግም፡፡ ወደ ቁም ነገሩ ልግባና የአንዱ ክለብ የእግር ኳስ ጨዋታ ሙያጠኛ /ፐሮፌሽናል የሚለውን የእንግሊዝኛ ቃለ ከተካልኝ/ በኮንስትራት ለተወሰነ ዓመት ከተሸጠበት ክለብ ወደ ሌላ ክለብ ተመልሶ ሲሸጥ ይሰተዋላል፡፡ ተጫዋቹም ይ ብዙ አያሳስባውም፡፡ ገንዘብ እስከተከፈለው ድረስ የሚሸጠው ክለብ አተረፈበት አላተረፈበትም፣ ለብዕናው ወደ ሸቀጥነት /ዘመና ባሪያነት/ መለወጡ ደንታዎ አይሰጠው፡፡ እንግዲህ ይህ ሁኔታ ህይወትን በማቆየት ውሳኜ ደረጃ ይለያይ እንጂ ከጥንቁ የባሪያ ፍንገላ በምን ይለይ? ያ የተሸጠ ተጨዋች ደገሞ ጨዋታው ከተቀነሰ ምንም ያህል ለክለቡ ውለታ የዋለ ቢሆን እንደ አሮጌ ቆርቆሮ መጣሉ አይቀሬ ነው፡፡ እርገትጥ በቁሳዊ ጥሪት መያዙና የባንክ ደብተሩ ላይ ቁጥሮች መነበባቸው ከሥጋዊ ምቾት ትንሽ ይጠቀመው ይሆናል፡፡ ነገር ገን ለሞራል ጎዳቱና ለህሊናዊ ጥያቄ ምን መልስ ይገኝለታል?
ሃሳቤን የበለጠ ግልፅ ለማድረግ አንድ ሌላ ምሳሌ ልጨምር፡፡ አኔሁ በለፀጉ የሚባሉ አገሮች ብዙ የተማረ ኃይል እንዳላቸው ይነገራል፡፡ የተማረውን ኃይል እንዴት አፈሩት ብንል ገን የሚኖረን መልስ በየሀገሩ ጥሩ ጭንቅላት ያለውን ምሁርን በተለያየ ዘዴ በማስኮብለል እያስቀሩት መሆኑን ደግሞ የተደበቀ ሁኔታ አለመሆኑን እንረዳለን፡፡
አነኝህ ምሁራን የሚኩበልሉበት ምክንያት ቢለያይም ከሀገር ወጪሄደው ቢሮሩ ገን በቁጭት እየተብሰለሰሉ አወዳደቃቸው እንደማያምር ይደመጣል፡፡ የቤተሰብ ናፍቆት፣ የሀገር ውበትና አየር፣ የደርጉበት ሰፈርና ጎደኖች፣ የተማሩበት ት/ቤና የልጅነት ፍቅረ በሃሳባቸው እየተመላለሰ ጤና እንደሚነሳቸው ከኖረበት ክ/ሀገር ወደ ሌላ በሥራም ሆነ በዕረፍት ለሄደ ሰው የሚረስ ነገር ስሆነ አዚህ ላይ ብዙ ማለት የሚስፈልግ አይመስለኝምም፡ አስገዳጅ ሁኔታዎችም እንደሚኖሩ አልዘነጋውም፡፡ ነገር ገን ለሰው ልጅ መብት ተከራካሪዎች ነን እያ በየመገናኘው ብዙሃን ባሸበረቁ ቃላቶች ዲማጉጋቸውን የሚለፍፉ ሀገሮች ከአንድ ወቅተ ጀምረው በሚያወግዙበት አፈቸው በየጊዜው በሚፈጠሩት ገደብ የለሽ ምንክያቶቻቸው በማደግ ላይ ያሉ አገሮን ምርት ዜጎች እየሸበቡ በዘማነው ባርነት ማድከማቸውና መጠፈራቸው የጥንተ ባርነት መልኩን ለውጦ እስከ ዘመናችን ድረሰ አልዘለቀም ለማለት የምንደፍር ሰንቶቻችን ነን? በአሜሪካ የጠፈር ምርምር ማዕከል ሆነ የመክላከያ ኃይል ተቋም በእውቀታቸው ተከብረው የሚሰሩ ምሁራን በራሳቸው ፍላጎት መልቀቅ ቢፈልጉ የመኖራቸው ዋስትና አደጋ ላይ መውደቁን ማሰብ ራሰ ጥንት በባርነት ከማቀቁ ሰዎች ልዩነቱ ምን ያህል የሰፋ ነው?
ከላይ ለመጠቃቀስ የሞከርኩት የሰው ልጅ ተፈጥሮን ለመለወጥ ባደረገው ትግል ብዙ ቢሳካለትም በራሱ የአስተሳሰብ አድማስ ነው ያደርገው ለውጥ ግን ሰው ሆኖ ከተፈጠረ ጀምሮ ብዙም ፈቅ አላለም ለማለት ነው፡፡ ግን ህይወት ምንድን ናት?
9
ህይወት? ክፍል 9
ብዙነሽ ወደ ቢሮ ስተወጣ ግቢዋን የሚጠበቅላት ላስቻለው የተባለውን ከትንሽነቱ ያሳደገችውን ውሻ ዘወትር እንደምታደርገው ደባብሰው እንገቱ ላይ ካለው ቀርቶ ጋር የታሰረበትን ሰንሰለት አላቀቀችለት፡፡ ላስቻለው እየፈነደቀ ግቢን አንዴ ከዞረ በኋላ ተመልሶ መጥቶ እግሯን ስር ተጋደመ፡፡ ዓይኗ እንባ አቅርሮ … መተኪያ… ብላ በቀስታ ተናግራ የግቡዋን በር ዘግታ ውጣች፡፡
ቢሮ አስከትደርስ የምታስላስለው የጓደኛዋ አስቴር ስለተላከላት የልደት ቀን ጥሪ ወረቀት ነበር፡፡ አስቴር ጋር ተኳርፈው ከተላያዩ ሦስት አመታቸውን ይዘዋል፡፡ አብሮ አደግ ጓደኛዋ ጋር የተከራረፈበት ጉዳይ ቀላል ቢሆንም ጥፋቱ የሷ ስላልሆነ በጣም አምርራ ተለይታታለች እየዋለ ሲያድር አስቴር ጥፋቷ ስለገባት በሰበቡም ይቅርታን ለማግኝት ሁለት ጊዜ በየዓመት የልደት በአሏ ላይ እንድተገኝላት ብትጠራትም ብዙነሽ … ካሁን ወዲህ ሰው ለምኔ… በማለት አልተበገረችላትም፡፡
…ላስቻለው… በሚል ስያሜ የምጠራውን ውሻም በህጻንነቱ ማሳደግ የጀመረችው ከምትወዳት ጎከኛዋ ጋር ተኮራርፋ ስተለያይ ሲሆን ለውሻው በግል …መተኪያ… ትለዋለች፡፡ የአብሮ አደግና የሚወዱት ጎደኛን ማስረሻ ለማሰለት፡፡
አብሮ አደግ ጓደኛዋ አስቴር አሁንም ሳትሰለች ለሦስተኛ ጊዜ በላከችላት የጥሪ ወረቀት በአጥሩ የእግዚአብሔር ይቅር ባይነት በማንሳት ይህንን ሶስት ዓመት ልቧ እያለቀሰ እንደተሰቃየችና ለመጨረሻ ጊዜ ጥሪውን እንደላከችላት የሚገልፅ የማስጠንቀቂያ ጽሁፍ ከግርጌው ሰፍሯል፡፡
በቢሮው የክፍል ኃለፊነቷ ብዙነሽ በቀልጣፋነቷ የተመሰገነች ቢሆንም በዛሬው ቀን በምትሰራው ሁሉ ነገር ላይ ፊቷ የኃዘን ደባብ እየተበበበትና እንዳንድ ጊዜም ትናንሽ ነገር ሁሉ እየረሳች ፀሐፊዋ ለአንድ ጉዳይ ሁለት ጊዜ መሳሳቷን ነግራታለች ከዚህ በኋላ ነበር ፀሐፊዋም ብዙነሽ ሰዎች አንዳይረብሿት ባለጉዳዮችን ለሌላ ጊዜ እየቀጠረች ያሰናበተቻቸው፡፡
ምሳ መድረሻ አካባቢ ስልክ ተደወለላት ከሃሳብ ማጥ ውስጥ አስበርግጎ ስወጣት ስልኩን ገላምጣው በንዴት ብድግ አደረገችው፡፡ ታዲዋስ ነው ከውሻዋ ቀጥሎ የምትወደው የወንድ ጎደኛዋ፡፡
ለምሳ ወጥቶ እንዲስዳት ከነገረቸው ሀኋላ ስልኩን በመዝጋት የሚደላው ወንበር ላይ ተደግፋ በረጅሙ ተነፈሰች፡፡ የቢሮ ጠረጴዛዋ ላይ በስጦታ ወረቀት ተጠቅልሎ ገብ ያለውን ናሽናል ፓናሶኒክ የሙዚቃ ማጫወቻ ቀኝ ላይ ዓይኗ ሲያርፍ ከሶስት ዓመት በፊት ስለተከሰተው ሁኔታ በትዝታ አስታውሰ ቁጭት ያበስላስላት ገባ፡፡
ያልተነጠፈው አልጋ ላይ ጋደም ብላ አስቴር ያዋስቻት ትንሽ ቴፕ የሚያንቆረቁረውን …አይ አዎ በሶሌንግ… የሚለወን የሮድ ስቴዋርት ዘፈን እያዳመጠች፡፡ ያልተነጠፈው አልጋ ስላልተመቻት ብድግ በማለት የአልጋ ልብስ፣ ብርድ ልብስ አንሶላ አነሳስታ ማንጠፍ ጀምራ ሳትጨርስ ከአልጋው አጠገብ በተቀመጠው ኮሜዲኖ ላይ ያለችው ትንሽ ቴፕ በብርድ ልብሱ አማካኝነት የሲሚንቶው ወለል ላይ ውብላ ወድቃ ብትንቅኗ ወጣ፡፡ ብዙነሽም ደነገጠች እየቆየችም ስትሄድ ደግሞ አይኗ ቲማቲም እስኪመስል አነባች፡፡ አስቴር ከወንድ ጎደኛዋ በስታ ያገኝቻትና የምትወዳት ቴፕ ነበረች፡፡ ብዙነሽ ለቅሶዋን ሳትጨርስ ለጎደኛዋ የቴፑን መርዶ በስልክ ስታደዳት አስቴር …በፍቅር ህይወቴ መጣሽብኝ ካሁን አንተዋወቅም አትድረሽብኝ… ነበር ያለቻት፡፡ ብዙነሽ ስልጁን ቀስ ብላ ዘግታ ስታስበው መናደዱን ተያያዘቸው፡፡
የቢሮው በር ተንኳክቶ ፀሐፊዋ የምሳ ሠዓት መድረሱን ስታበስራት ነበር ከትዝታዋ የተመለሰችው ብዙነሽ ለፀሐፊዋ መልሰካም የእረፈት ቀን ተመኝታላት በአንድ እጇን የስጦታውን ፓኬት በሌላው ቦርሳዋን ትከሻዋ ላይ ጣል አድርጋ ስትወጣ ፀሐፊዋ ፓኬቱን ልትረዳት እንደምትችል ብታስታውሳትም ግድ የልመ… የሚል ሰጥታች በችኮላ ተንደረዳረች፡፡ የመ/ቤቷን የውጪ በር እንደወጣች ታዲዎስን አመኪናው ውስጥ እንደተቀመጠ አየችው መኪናው ጋር ደርሳ በሩን ከፍታ እንደገባች በልቧ የመነኩሰች ልዕልቴ ሰላምታዬ ይድረስሽ… በማለት ሳም አደረጋትና ጭኗ ላይ ያለውን የስጦታ ዕቃ ተመልከቶ መኪናውን አንቀሳቀሰው፡፡
ሆቴል ግብተው መሳ ቀርቦላቸው ሁሉ ዝምታ ሰፍኗል በመሃላቸው፡፡ ከምሳ በኋለ ቡና እየጠጡ ሳለ … በመጨረሻ ልታረቃት ወሰንኩ… አለችው ብዙነሽ የቡናውን ስኒ ማስቀመጫው ላይ እንዳለ አያሸከረከረች፡፡
ታዲዎ ብዙ ጊዜ ስለአብሮ አደግ ጎደኛዋ አጫውታዋለች፡፡ ስለ አስቴር አውርታ አትጠግብም፡፡ ነገር ገን ሁሉት ዓመት ሜሎ ልደታ ላይ እንድትገኝ ስትጠራት ወሳኔዋ ቁጥር ነበር፡፡ በአስቴር የልደት ቀን ግን ብዙነሽ ስታለቅስ ነው ያሳለፈችው፡፡ የዘንድሮውን ግን ልትሄድ ወሰናለች፡፡ የስጦታ ዕቃዎ አዘጋጅታላታለች፡፡
…ግሩም ነው… …በዛሬ ታላቃ ቀን ገን እኔም ብገኝ ምንኛ ደስ ባለኝ እነዚያ ጅቦች አስችኳይ ስብሰባ ጠርተዋል፡፡… አለና ሲና ደድ እንደያደርገው እጅን አወናጨፈ ‹ጅቾች› የሚላቸው አለቆቹን ነው፡፡
…በታክሲ ልሄድነው እንዴ ታዲያ ዘጠኝ ሰዓት ላይ ነውኮ ጥሪው?... አፈጠጠችበት
የገንዘብ ቦርሳውን አወጥቶሄሳቡን ጠረጴዛው ላይ ካኖረ በኋላ ከመቀመጫው እየተነሳ …አንቺ መ/ቤት ታደርሺኝና መኪናዋን ይዘሽ ትሄዳለሽ፡፡ አላት ትከሻዋ ላይ እጁን ጣል አድርጎጎ፡
…ዛሬ እንኳን መሪ ባልይዝ ይሻል ነበር፡፡ ቸግር ከሆነ ግን ምን ይደረግ፡፡… በማለት የመኪናወውን ቁልፍ ተቀበላ በሹፊሩ መግቢ በኩል ገብታ ለሱም በሩን ከፍተችለት፡፡
መ/ቤቱ አድርሳው ቶሎ ከጨረሰ ከቤቷ እንዲጠብቃት ከነገረችው በኋላ …መተኪያ… ለምትለው ውሻዋ የአሁድ ቀለቡን ከተኮናተረችለት ቦታ በመያዝ ውሻዋን ለማየትና ከዚያም ልብስ ለመቀየር ወደ ቤቷ ከነፈች፡፡
ቤቷ በር ላይ ደርሳ መኪናዋን እንደቆመች የተሰበሰቡት ሰዎ ሲጠቃቀሱባት አስተውላ ነበር እንዳለ ገባት፡፡ ሁለት ፖሊሶች ወደ እሷ ተጠግታው ሰላምታ ሰጥተዋት ለምርመራ እንደሚልጓት ነገረው ፖሊስ ጣቢ ወሰዷት፡፡ ለጥያቄ ስምንት ሰዓት የሄደች …ስልክ እንኳን ልደውል፡፡… እባካችሁ አድራሻዬን እንኳ ለዘመድ ንገሩል …እያለች ብትወተወትም ለጥያቄዋ መልስ ያገኝቸውና በዋሰ የተፈታቸው ከጠዋቱ በሦስት ነው፡፡ የታሰረችበት ምክንያት ያትም ውሻዋ …መተኪያ… ኳስ ሊያወጣ በአጥር ዘሎ ግቢዋ የገባውን የጎረቤት ጎረምሳ ስለነከሰ ነበር፡፡ቀን የጠፋን በሬና የሚሰርቅ ሌባን ያገናኛል፡፡.. እንዲሉ፡፡ ግን ህይወት ምንድን ናት?
8
ህይወት? ክፍል 8
ዘመን ዘመንን እየተካ ሲሄድ ትውልዱም እንዲሁ ተክቶ ማለፍ አይቀሬ ነው ከዘመን ጋር አብረው የሚስወጡተፈጥሮዊም ሆኑ ማህበራዊ ክስተቶች በየትውልዱ ላይ ከሚያትሙት አሻራ ለቀጣዩ ትውልዱ ስብዕና ወሳኝነት አላቸው፡፡
ከአያቶችን ዘመን ስንነሳ ሰዎች በየተሰማሩበት መስክ ለፍተው ደክበመው የተገኝውን እነሱም በዛ ከቤተሰብ ተከፍለው፣ ከሥራ ውጪም ከዕድአኩዮቻቸው ጋር ፀጋቸውን አውግተው /ለልማት ሥልም ሆነ ለሽምግናል/ አደባባይ ውለው አመሻሽተው ይገባሉሉ፡
የነሱ ልጆ /የኛ ወላጆች ማለት ነው፡፡/ ከብት አያገዱ ወይንም ሌላ ስራ እየሰሩ የልጅነት ጨዋታችውን ከጓደኖቻቸው ጋር ተዋዘተው አሳልፈውታል፡፡ ከፍ እያሉም ሲሄድ የቤተ ህክነት የትመህርተን ቀስመው አሌም የቤተሰቢቻቸው ዱካ ተከትለው ከጠነከሩ በኋለ በየስራ መስኩ ተስርተዋል፡፡ ገበሬውም ወደ እርሻው፣ ነጋዴውም ወደ ንግዱ፣ ወደ ወትድርና ወደ እጅጥበብና ሌላም ሌላም ሙያዎች ላይ በመሰማራት ቤተሰብ መስርተው እናነ ተክተዋል፡፡
የድሮ ሰው ኩራቱ ተተኪ ልጅ ማፍራተቱ ነው ይባላል፡፡ … ተተኪልጅ… ታዲያ በዘመኑ የነበሩ የራሱ መስፈሪያ ነበረው፡፡ እግዚአብሔርን ፈሪ፣ ሰውን አክባሪ፣ ወላጆቱን ጧሪ የሚሉት ሐረጎች ከነበሩት መመሪያዎች ይደመራሉሉ፡
እናም እንግዲ ት/ቤት ገብተን፣ከዚህም ሥራ ላይ በመሰማራት እየተፈጨረጨርን ሲሆን ዘመናችን ግግ በብዛው መልኩ በቴክኖሎጂ እየታገዘ ወላጆቻችን ከኖሩበት ይልቅ ኑሮን የተቃለለ አድርጎልናል፡፡ ይህ ፈጣን የቴክኖሎጂ ዘመን ግን የነጠቀንም ሀብቶች ትንሽ አይደለም፡፡ ባህላችንን፣ እና የመኖር ዋስትናችን ለዋቢነት በቂ ናቸው ብዬ አስባለሁ፡፡
ወላጆቻችን ሃይኖታችውን ይዘው ርጋታ በሞላበት ኑሮ ዘመኑ በፈቃደው ሁኔታ መና ብሎው ኖረዋል፡፡ እኛ ደግሞ ከቴክኖሎጂ ወጣቶች ሁካታ ጋር ርካታም ሳናጋኝ እንደተነጫነጭን እንዳለን አለን፡፡ ጊዜው ከመጠቀም አኳያ ወላጆቻችንም እኛም ዛሬን እንደሰት በሚለው ዘይቤያቸን ጊዜውን ቁም ነገር ሳንሰራበት አያሳርፍ ነው፡፡
ምናልባት እኛ ከተዘናጋንበት ለመንቃት አሁንም ጊዜ አለን፡፡ ነገር ግን የተበታተነውን ትኩረታችንን አሰባስበን በመወያየት አንድ ነገር መጀመር አለብን፡፡ ወቅቱ እያለፈብን ከሄደ ለልጆቻችን የምናወርሰው ጉዳት ልጆቻችንን ወደፊት የሚያሳርፍ እንዳይን ጥረቱ ከዛሬው ይጠበቅብናል፡፡
ልጆቻችን የሚኖሩበትን አካባቢ አለፍ ብለውም ሀገራቸውንላቅ ሲልም ዓለማችንን በጊዜው እንዲውቁና ለማህበራዊ ኑሮ ጥሩ እውቀት እንዲኖራቸው በቤትም ሆነ በት/ቤትም የቀን ተቀን ክትትል ያስፈልጋቸዋል፡፡
ከሀገራችን ጥያቃዊነት አኳያ ዘሬ ያለንበት ሁኔታ በተለያየ መድረከ ሲገመገም ብዙም ፈቅ አለማለቱ ለምንድን ነው? የሚለው ጥያቄ ከህሊና ወጥቶ በአደባባይ የታረክ ሊቃውንት፣ የስነ-ልቡና ጠበብቶች፣ ሌሎችም የማህበራዊ ሳይንስ ጠበብቶች ሊነጋገሩበት የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡ በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ጭንቅላት እየተገገዋለለም ዐማታት መቁረ አሁንም የቀጣይን ትውልድ ዓይን ሽፍኖ ራስንችለህ ሄድ ከማለት አይለይም፡፡
አያቶቻችነ ኖረው አልፈዋል፡፡ ወላጆቻችንም ሲሰሩ የሚችሉበትን ጊዜ ጨርሰውታል፡፡ ነገር ግን ለልቻቸው የሚነገሩትና ለለንበት ደረጃ ምክንያት የሚሆን አያሌ አውነታዎችን ለመሰክሩልን ይችላሉና የቀራቸውን ጌዜ ከመጠቀም ባንቀጥብ ብልህነት ይመስለኛል፡፡ እኛም የተወሰነ መሰሪያ ጊዜ አለን፡፡ /የት ለመድረሰ ካልተባልኩ፡፡/ ለልጆቻችን ዋና ቀናውን ካሁን ማውረስ መቻል ተገቢነው ባይነኝ ገን ህይወት ምንድን ናት?