ህይወት? ክፍል 9
ብዙነሽ ወደ ቢሮ ስተወጣ ግቢዋን የሚጠበቅላት ላስቻለው የተባለውን ከትንሽነቱ ያሳደገችውን ውሻ ዘወትር እንደምታደርገው ደባብሰው እንገቱ ላይ ካለው ቀርቶ ጋር የታሰረበትን ሰንሰለት አላቀቀችለት፡፡ ላስቻለው እየፈነደቀ ግቢን አንዴ ከዞረ በኋላ ተመልሶ መጥቶ እግሯን ስር ተጋደመ፡፡ ዓይኗ እንባ አቅርሮ … መተኪያ… ብላ በቀስታ ተናግራ የግቡዋን በር ዘግታ ውጣች፡፡
ቢሮ አስከትደርስ የምታስላስለው የጓደኛዋ አስቴር ስለተላከላት የልደት ቀን ጥሪ ወረቀት ነበር፡፡ አስቴር ጋር ተኳርፈው ከተላያዩ ሦስት አመታቸውን ይዘዋል፡፡ አብሮ አደግ ጓደኛዋ ጋር የተከራረፈበት ጉዳይ ቀላል ቢሆንም ጥፋቱ የሷ ስላልሆነ በጣም አምርራ ተለይታታለች እየዋለ ሲያድር አስቴር ጥፋቷ ስለገባት በሰበቡም ይቅርታን ለማግኝት ሁለት ጊዜ በየዓመት የልደት በአሏ ላይ እንድተገኝላት ብትጠራትም ብዙነሽ … ካሁን ወዲህ ሰው ለምኔ… በማለት አልተበገረችላትም፡፡
…ላስቻለው… በሚል ስያሜ የምጠራውን ውሻም በህጻንነቱ ማሳደግ የጀመረችው ከምትወዳት ጎከኛዋ ጋር ተኮራርፋ ስተለያይ ሲሆን ለውሻው በግል …መተኪያ… ትለዋለች፡፡ የአብሮ አደግና የሚወዱት ጎደኛን ማስረሻ ለማሰለት፡፡
አብሮ አደግ ጓደኛዋ አስቴር አሁንም ሳትሰለች ለሦስተኛ ጊዜ በላከችላት የጥሪ ወረቀት በአጥሩ የእግዚአብሔር ይቅር ባይነት በማንሳት ይህንን ሶስት ዓመት ልቧ እያለቀሰ እንደተሰቃየችና ለመጨረሻ ጊዜ ጥሪውን እንደላከችላት የሚገልፅ የማስጠንቀቂያ ጽሁፍ ከግርጌው ሰፍሯል፡፡
በቢሮው የክፍል ኃለፊነቷ ብዙነሽ በቀልጣፋነቷ የተመሰገነች ቢሆንም በዛሬው ቀን በምትሰራው ሁሉ ነገር ላይ ፊቷ የኃዘን ደባብ እየተበበበትና እንዳንድ ጊዜም ትናንሽ ነገር ሁሉ እየረሳች ፀሐፊዋ ለአንድ ጉዳይ ሁለት ጊዜ መሳሳቷን ነግራታለች ከዚህ በኋላ ነበር ፀሐፊዋም ብዙነሽ ሰዎች አንዳይረብሿት ባለጉዳዮችን ለሌላ ጊዜ እየቀጠረች ያሰናበተቻቸው፡፡
ምሳ መድረሻ አካባቢ ስልክ ተደወለላት ከሃሳብ ማጥ ውስጥ አስበርግጎ ስወጣት ስልኩን ገላምጣው በንዴት ብድግ አደረገችው፡፡ ታዲዋስ ነው ከውሻዋ ቀጥሎ የምትወደው የወንድ ጎደኛዋ፡፡
ለምሳ ወጥቶ እንዲስዳት ከነገረቸው ሀኋላ ስልኩን በመዝጋት የሚደላው ወንበር ላይ ተደግፋ በረጅሙ ተነፈሰች፡፡ የቢሮ ጠረጴዛዋ ላይ በስጦታ ወረቀት ተጠቅልሎ ገብ ያለውን ናሽናል ፓናሶኒክ የሙዚቃ ማጫወቻ ቀኝ ላይ ዓይኗ ሲያርፍ ከሶስት ዓመት በፊት ስለተከሰተው ሁኔታ በትዝታ አስታውሰ ቁጭት ያበስላስላት ገባ፡፡
ያልተነጠፈው አልጋ ላይ ጋደም ብላ አስቴር ያዋስቻት ትንሽ ቴፕ የሚያንቆረቁረውን …አይ አዎ በሶሌንግ… የሚለወን የሮድ ስቴዋርት ዘፈን እያዳመጠች፡፡ ያልተነጠፈው አልጋ ስላልተመቻት ብድግ በማለት የአልጋ ልብስ፣ ብርድ ልብስ አንሶላ አነሳስታ ማንጠፍ ጀምራ ሳትጨርስ ከአልጋው አጠገብ በተቀመጠው ኮሜዲኖ ላይ ያለችው ትንሽ ቴፕ በብርድ ልብሱ አማካኝነት የሲሚንቶው ወለል ላይ ውብላ ወድቃ ብትንቅኗ ወጣ፡፡ ብዙነሽም ደነገጠች እየቆየችም ስትሄድ ደግሞ አይኗ ቲማቲም እስኪመስል አነባች፡፡ አስቴር ከወንድ ጎደኛዋ በስታ ያገኝቻትና የምትወዳት ቴፕ ነበረች፡፡ ብዙነሽ ለቅሶዋን ሳትጨርስ ለጎደኛዋ የቴፑን መርዶ በስልክ ስታደዳት አስቴር …በፍቅር ህይወቴ መጣሽብኝ ካሁን አንተዋወቅም አትድረሽብኝ… ነበር ያለቻት፡፡ ብዙነሽ ስልጁን ቀስ ብላ ዘግታ ስታስበው መናደዱን ተያያዘቸው፡፡
የቢሮው በር ተንኳክቶ ፀሐፊዋ የምሳ ሠዓት መድረሱን ስታበስራት ነበር ከትዝታዋ የተመለሰችው ብዙነሽ ለፀሐፊዋ መልሰካም የእረፈት ቀን ተመኝታላት በአንድ እጇን የስጦታውን ፓኬት በሌላው ቦርሳዋን ትከሻዋ ላይ ጣል አድርጋ ስትወጣ ፀሐፊዋ ፓኬቱን ልትረዳት እንደምትችል ብታስታውሳትም ግድ የልመ… የሚል ሰጥታች በችኮላ ተንደረዳረች፡፡ የመ/ቤቷን የውጪ በር እንደወጣች ታዲዎስን አመኪናው ውስጥ እንደተቀመጠ አየችው መኪናው ጋር ደርሳ በሩን ከፍታ እንደገባች በልቧ የመነኩሰች ልዕልቴ ሰላምታዬ ይድረስሽ… በማለት ሳም አደረጋትና ጭኗ ላይ ያለውን የስጦታ ዕቃ ተመልከቶ መኪናውን አንቀሳቀሰው፡፡
ሆቴል ግብተው መሳ ቀርቦላቸው ሁሉ ዝምታ ሰፍኗል በመሃላቸው፡፡ ከምሳ በኋለ ቡና እየጠጡ ሳለ … በመጨረሻ ልታረቃት ወሰንኩ… አለችው ብዙነሽ የቡናውን ስኒ ማስቀመጫው ላይ እንዳለ አያሸከረከረች፡፡
ታዲዎ ብዙ ጊዜ ስለአብሮ አደግ ጎደኛዋ አጫውታዋለች፡፡ ስለ አስቴር አውርታ አትጠግብም፡፡ ነገር ገን ሁሉት ዓመት ሜሎ ልደታ ላይ እንድትገኝ ስትጠራት ወሳኔዋ ቁጥር ነበር፡፡ በአስቴር የልደት ቀን ግን ብዙነሽ ስታለቅስ ነው ያሳለፈችው፡፡ የዘንድሮውን ግን ልትሄድ ወሰናለች፡፡ የስጦታ ዕቃዎ አዘጋጅታላታለች፡፡
…ግሩም ነው… …በዛሬ ታላቃ ቀን ገን እኔም ብገኝ ምንኛ ደስ ባለኝ እነዚያ ጅቦች አስችኳይ ስብሰባ ጠርተዋል፡፡… አለና ሲና ደድ እንደያደርገው እጅን አወናጨፈ ‹ጅቾች› የሚላቸው አለቆቹን ነው፡፡
…በታክሲ ልሄድነው እንዴ ታዲያ ዘጠኝ ሰዓት ላይ ነውኮ ጥሪው?... አፈጠጠችበት
የገንዘብ ቦርሳውን አወጥቶሄሳቡን ጠረጴዛው ላይ ካኖረ በኋላ ከመቀመጫው እየተነሳ …አንቺ መ/ቤት ታደርሺኝና መኪናዋን ይዘሽ ትሄዳለሽ፡፡ አላት ትከሻዋ ላይ እጁን ጣል አድርጎጎ፡
…ዛሬ እንኳን መሪ ባልይዝ ይሻል ነበር፡፡ ቸግር ከሆነ ግን ምን ይደረግ፡፡… በማለት የመኪናወውን ቁልፍ ተቀበላ በሹፊሩ መግቢ በኩል ገብታ ለሱም በሩን ከፍተችለት፡፡
መ/ቤቱ አድርሳው ቶሎ ከጨረሰ ከቤቷ እንዲጠብቃት ከነገረችው በኋላ …መተኪያ… ለምትለው ውሻዋ የአሁድ ቀለቡን ከተኮናተረችለት ቦታ በመያዝ ውሻዋን ለማየትና ከዚያም ልብስ ለመቀየር ወደ ቤቷ ከነፈች፡፡
ቤቷ በር ላይ ደርሳ መኪናዋን እንደቆመች የተሰበሰቡት ሰዎ ሲጠቃቀሱባት አስተውላ ነበር እንዳለ ገባት፡፡ ሁለት ፖሊሶች ወደ እሷ ተጠግታው ሰላምታ ሰጥተዋት ለምርመራ እንደሚልጓት ነገረው ፖሊስ ጣቢ ወሰዷት፡፡ ለጥያቄ ስምንት ሰዓት የሄደች …ስልክ እንኳን ልደውል፡፡… እባካችሁ አድራሻዬን እንኳ ለዘመድ ንገሩል …እያለች ብትወተወትም ለጥያቄዋ መልስ ያገኝቸውና በዋሰ የተፈታቸው ከጠዋቱ በሦስት ነው፡፡ የታሰረችበት ምክንያት ያትም ውሻዋ …መተኪያ… ኳስ ሊያወጣ በአጥር ዘሎ ግቢዋ የገባውን የጎረቤት ጎረምሳ ስለነከሰ ነበር፡፡ቀን የጠፋን በሬና የሚሰርቅ ሌባን ያገናኛል፡፡.. እንዲሉ፡፡ ግን ህይወት ምንድን ናት?
No comments:
Post a Comment