ህይወት? ክፍል 6
በሃገራችን የእግር ኳስ ስፖርት ሲነሳ አብረው የሚነሱ ስፖርተኛ ከጅምሩ አሁን እስካለበት ድረስ ያደረሱ፣ ከሃገርም አልፈው በአህጉና በዓለም በከፍተኛ ደረጃ የታወቁና ከብር የተለረሳቸው ድንቅ ክቡር አቶ ይድቃቸው ተሰማ ይጠቀሳሉሉ፡ የአንጋፋው የስፖርት ሰው በአካል ባናገኛቸውም የህይወት እያሉ የፈጸሟቸውና እየጉላ ነው፡፡ …ስፖርትና ጎጂ ባህሎች ሌጣመሩ አይገባም ስለዚህም በስተዲየሞች ያሉ የጎጂ ሱስ ማስታወቂያዎች መነሳት አለባቸው፡፡ … አፍሪካን በዓለም አቀፍ እግር ኳስ ዋንጫ የሚወከሉ ቡድኖች ቁጥራቸው ከፍ ማለት አለበት… የሚሉት ነጥቦችን ማቅረብ ለቅሱስ ዓላማቸው ቁርጠኛነታቸውን ሲያሳዩ የሚችሉ ምሳሌዎች ናቸው፡፡
እንዲያውም ቅዱስ መጽሐፍ ላይ … ነብይ በእግሩ አይከበርም… እንዲሉ ካልነ በቀር ለክቡር አቶ ይድነቃቸው መታሰቢያ እስካሁን እንድም አለ መደረጉ ወይም ሲመከር አለመስቱ ወይ ጊዜ፣ ወይ ጊዜ እያሰኝ የስፖርት ቤተሰቦችን ማንገብገቡ በብዙ ቦታ ይደመጣል፡፡ በዓለም ደረጃ ብዙ የተነገረላቸው እኚህ … የጀብራልተሩ አለት… ሞሮኮ ውስጥ አንዱ ስቴዲየም በስማቸው መሰየሙ ለኛ ፌዴሬሽን ጆሮ አልደረሰ ይሆን?
ከእግር ኳስ ስፖርት ሳንወጣ የጊዮርጊን ሺ መለያ ቁጥር 8/ን/ ለብሶ የጎል አካባቢውን ሜዳ /ቃላቶቻችን እንደሚያስታውሱት/ በቁጥጥሩ ሥር የሚያደርገው የጎል ካፒታኑ መንግስት ወርቁ ጨዋታም ካቋረጠ በኋላ በአሰልጣኝነት ገፍቶበት ከአፍሪቃ አሠልጣኞች ቀዳሚነቱን ደረጃ የያዘ በሙያው አንቱ የተባለ ሆኖ በተወለደበት ሀገር ላይ ግን ለ ጡረታ መሰናበት አያደር መገረሙ አይቀርም፡፡
ያደላቸው ቸሎታ ያለውን ከሌላ ሀገርም ቢሆን ለምነው፣ ተደራድረውና ተንከባክበው ያስሩታል፡፡ ከእኛው ሀገር ግን የሀገሪቱን ብርቅ ልጆች የሚያቆሉ ሁኔታዎ ገጥመውናል፡፡ አረ ወገን ዜው ካለፈ በዋዛ የሚተኩ ሰዎች አይደሉምና ተገቢውን ትኩረት እንንፈጋችው፡፡
ስለክቡር አቶ ይድነቃቸው የአለም ጋዜጠኞች የመሰከሩላቸው ራሱ ትልቅ ግምት የሚሰጠው ነው፡፡ …ከመቀረት መዘግየት… ይሻላልና እንተባበር፡፡
ከሀገር ወጣ ብለን ደግሞ እሰኪ ወደ ዓለም አቀፍ የእግር ኳስ አሬና ላይ ባለፉት ቅርብ ዓመታት ሲወደስና አብረውት ከሚጫወቁት ግዝፎ የወጣውን ማራዶናን ለአፍታ እናስበው፡፡
ይህ የአረጀንቴናው ተወላጅ ዲዮጎ ማራዶና በዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ የሀገሩ ስም ሁለት ጊዜ ያስጠራ የሀገሪቱ ብርቅ ልጅ ነው፡፡ በጨዋታው ድንበር ተሸግሮና ውቅያኖስን አቋርቶ ጣልያን ክለቦች ረዘም ላለ ጊዜ ሲጫወት በዓለም ላይ ስ ከዳር እስከዳር ናኝቷል፡፡ ሀብፈትም ጉርፎለታል፡፡ በስፖርት ዕቃዎችና የተለያዩ ነገሮች ላይ ስሙን ማስተዋወቁም አድርጎ ተዝቆ የማያልቅ አግኝቶበታል፡፡ ለማራዶና ኑሮ ግን ብዙም አልተመቸውም፡፡ በፍቅሩ ወይንም በግንዘቡ የተጠመዱ ሴቶች አላስወጣ አላስገባ እያሉትና ሁለቱ ያህልም ይወስዳል በሚል ክስ ፍዳ መክራውን አይቷል፡፡ የማፊያ ቡድንም ዋ አያለው ቆይቷል፡፡ በእግር ኳስ ከፍተኛ ዝነኛ ሀብት ያገኛው ማራዶና ስሙ በቤትና በሃሺሽ ተበጠልጥሏ፡፡ ኑሮ የሚባለው አባዜ ትንሹንም ትልቁንም በትለያዩ ሁኔታዎች አያሠጋው ነው፡፡ ግን ህይወት ምንድን ናት?
No comments:
Post a Comment