ህይወት ክፍል 11
የሰው ልጅ በኖረባቸው ብዙ ሺኅ ዓመታት በተፈጥሮ ያደረገው ዝግመታዊ ለውጥና ከተፈጥሮ ጋር ባደረገው ፍጥጫ የደረሰባቸው የቴክኖሎጂ ውጪቶች የሚያስደንቁን ቢንም እንዳንድ ጊዜ ገን ግራ እያጋቡን ይጋኛሉ፡፡
ከቻርሊስ ዳር ዊን ቴዎሪ ተነስተን የሰውን ልጅ በራሱ ላይ በተፈጥሮ ክስተቶች በመታገዝ ያደረገውን ዝግመት ለውጥ ሰናይ በማህበረሰብ በመሰባሰበብ ያሳለፈውን ህይወትና የማህበረሰቡን የዕድገት ደረጃ እንደናጢን መገደዳችን አሌ አይባልም፡፡
በኢትዮጵያችን እንኳ ባሪያ መሸጥ መለወጥ እንዲቆም በአዋጅ ደረጃ /በተገበር ላይ ከአዋጁ በኋላም ቆቶ ተሰተዋሏልና፡፡/ በአፄ ሚኒሊክ ጊዜ ነው የተደረገገው፡፡ /ይህ የባሪያ ፍንግሌ ግን በዘመናዊ መልክ ቀጥሎ የመኖር እስትንፋሱ በተወሰነ ደረጃ ቀይሮ ባሪያ የነበረው ሠራተኛ ተሰጥቶ ይገኛል፡፡/ እዚህ ላይ አማረኛ ቋንቋ ስሚችግረኝ ለቃላት አጠቃቀሜ እንባቢን ይቅርታ እጠይቃለሁ፡፡/
በቴክኖሎጂና ብሔራዊ ሀብት መጠን በልፀገዋል በሚባሉት ሀገሮች ሁሉ የባሪያ ፍንግሌ /ያላችሁትን በሉኝ እንጂ/ እንደቀጠለ ነው ያለው፡፡ እዚህ ላይ ምሳሌ ብጠቅስ ሃሳቤን ግልፅ ያደርገዋልና እንካችሁ፡፡
ለሞኑን የዓለም ዋንጫ እተካሄደ ነው፡፡ እኔ እንኳን ጥሩ የእግር ኳስ ጥበብ ለማየት ብቻ ሰምቼ እያለሁ እንጂ በቀን በቀን የአንቀጽ ልፍ ሰዓቱን እንዲሻብብቅ አልፈልግም፡፡ ወደ ቁም ነገሩ ልግባና የአንዱ ክለብ የእግር ኳስ ጨዋታ ሙያጠኛ /ፐሮፌሽናል የሚለውን የእንግሊዝኛ ቃለ ከተካልኝ/ በኮንስትራት ለተወሰነ ዓመት ከተሸጠበት ክለብ ወደ ሌላ ክለብ ተመልሶ ሲሸጥ ይሰተዋላል፡፡ ተጫዋቹም ይ ብዙ አያሳስባውም፡፡ ገንዘብ እስከተከፈለው ድረስ የሚሸጠው ክለብ አተረፈበት አላተረፈበትም፣ ለብዕናው ወደ ሸቀጥነት /ዘመና ባሪያነት/ መለወጡ ደንታዎ አይሰጠው፡፡ እንግዲህ ይህ ሁኔታ ህይወትን በማቆየት ውሳኜ ደረጃ ይለያይ እንጂ ከጥንቁ የባሪያ ፍንገላ በምን ይለይ? ያ የተሸጠ ተጨዋች ደገሞ ጨዋታው ከተቀነሰ ምንም ያህል ለክለቡ ውለታ የዋለ ቢሆን እንደ አሮጌ ቆርቆሮ መጣሉ አይቀሬ ነው፡፡ እርገትጥ በቁሳዊ ጥሪት መያዙና የባንክ ደብተሩ ላይ ቁጥሮች መነበባቸው ከሥጋዊ ምቾት ትንሽ ይጠቀመው ይሆናል፡፡ ነገር ገን ለሞራል ጎዳቱና ለህሊናዊ ጥያቄ ምን መልስ ይገኝለታል?
ሃሳቤን የበለጠ ግልፅ ለማድረግ አንድ ሌላ ምሳሌ ልጨምር፡፡ አኔሁ በለፀጉ የሚባሉ አገሮች ብዙ የተማረ ኃይል እንዳላቸው ይነገራል፡፡ የተማረውን ኃይል እንዴት አፈሩት ብንል ገን የሚኖረን መልስ በየሀገሩ ጥሩ ጭንቅላት ያለውን ምሁርን በተለያየ ዘዴ በማስኮብለል እያስቀሩት መሆኑን ደግሞ የተደበቀ ሁኔታ አለመሆኑን እንረዳለን፡፡
አነኝህ ምሁራን የሚኩበልሉበት ምክንያት ቢለያይም ከሀገር ወጪሄደው ቢሮሩ ገን በቁጭት እየተብሰለሰሉ አወዳደቃቸው እንደማያምር ይደመጣል፡፡ የቤተሰብ ናፍቆት፣ የሀገር ውበትና አየር፣ የደርጉበት ሰፈርና ጎደኖች፣ የተማሩበት ት/ቤና የልጅነት ፍቅረ በሃሳባቸው እየተመላለሰ ጤና እንደሚነሳቸው ከኖረበት ክ/ሀገር ወደ ሌላ በሥራም ሆነ በዕረፍት ለሄደ ሰው የሚረስ ነገር ስሆነ አዚህ ላይ ብዙ ማለት የሚስፈልግ አይመስለኝምም፡ አስገዳጅ ሁኔታዎችም እንደሚኖሩ አልዘነጋውም፡፡ ነገር ገን ለሰው ልጅ መብት ተከራካሪዎች ነን እያ በየመገናኘው ብዙሃን ባሸበረቁ ቃላቶች ዲማጉጋቸውን የሚለፍፉ ሀገሮች ከአንድ ወቅተ ጀምረው በሚያወግዙበት አፈቸው በየጊዜው በሚፈጠሩት ገደብ የለሽ ምንክያቶቻቸው በማደግ ላይ ያሉ አገሮን ምርት ዜጎች እየሸበቡ በዘማነው ባርነት ማድከማቸውና መጠፈራቸው የጥንተ ባርነት መልኩን ለውጦ እስከ ዘመናችን ድረሰ አልዘለቀም ለማለት የምንደፍር ሰንቶቻችን ነን? በአሜሪካ የጠፈር ምርምር ማዕከል ሆነ የመክላከያ ኃይል ተቋም በእውቀታቸው ተከብረው የሚሰሩ ምሁራን በራሳቸው ፍላጎት መልቀቅ ቢፈልጉ የመኖራቸው ዋስትና አደጋ ላይ መውደቁን ማሰብ ራሰ ጥንት በባርነት ከማቀቁ ሰዎች ልዩነቱ ምን ያህል የሰፋ ነው?
ከላይ ለመጠቃቀስ የሞከርኩት የሰው ልጅ ተፈጥሮን ለመለወጥ ባደረገው ትግል ብዙ ቢሳካለትም በራሱ የአስተሳሰብ አድማስ ነው ያደርገው ለውጥ ግን ሰው ሆኖ ከተፈጠረ ጀምሮ ብዙም ፈቅ አላለም ለማለት ነው፡፡ ግን ህይወት ምንድን ናት?
No comments:
Post a Comment